Facebook o girmay reda

Powered By Blogger

Followers

Tuesday, August 9, 2022

የሹመት ዜና

አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) የአደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) በቅርቡ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከሥልጣን በተነሱት የቀድሞ የአደጋ ሥጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ ምትክ ለአምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) የኮሚሽነርነት ሥልጣን ሰጡ፡፡ የኮሚሽኑ ምንጮች ለሪፖርተር እንዳረጋገጡት የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዛሬ ማክሰኞ ነሐሴ 3 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደ ኮሚሽኑ የላከው ደብዳቤ አምባሳደር ሽፈራው (ዶ/ር) ከሐምሌ 29 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ ኮሚሽነር ሆነው እንደተሾሙ አስታውቋል፡፡ አምባሳደር ሽፈራው (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትርና ትምህርት ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ደግሞ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የኢትዮጵያ አምባሳደርና እንዲሁም የሌሴቶና ናሚቢያ አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል፡፡ ምንጭ Reporter @EliasMeseret

Sunday, August 7, 2022

ኢትዮጵያ የደመቀችበት

በኮሎምቢያ ካሊ በተካሄደው የአለም ከ20 አመት በታች ሻምፒዮና በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ኢትዮጵያ የደመቀችበት፣ የማይረሳ ታሪካዊ ምሽት! 3ኛው🥇ወርቅ በ1500 ሜትር ሴቶች ብርቄ ሀየሎም 4ኛው🥇ወርቅ በ800 ሜትር ወንዶች ኤርሚያስ ግርማ 5ኛው🥇ወርቅ በ5000 ሜትር ሴቶች መዲና ኢሳ 6ኛው🥇ወርቅ በ3000 ሜትር ወንዶች መሰናክል ሳሙኤል ዱጉና 4ኛው🥈ብር በ5000 ሜትር ሴቶች መልክናት ውዱ 5ኛው🥈ብር በ3000 ሜትር ወንዶች መሰናክል ሳሙኤል ፍሬው ድንቅ ምሽት፣ ኢትዮጵያ ከፍ ያለችበት፣ በደቂቃዎች ውስጥ በተለያዩ ውድድሮች ወርቅ የጠራረገችበት ድንቅ ምሽት፣ 4 ወርቅ 2 የብር ሜዳሊያዎችን በሰዓታት ውስጥ! (via Temesgen Yifru) በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ውድድሩን ከአሜሪካ እና ጃማይካ በመቀጠል በሶስተኛነት አጠናቃለች። እንኳን ደስ አላችሁ፣ አለን! ምንጭ @EliasMeseret

Thursday, October 14, 2010

Sunday, January 31, 2010

crated by Girmay Reda



Beauty of Mathematics !!!!!!!

1 x 8 + 1 = 9
12 x 8 + 2 = 98
123 x 8 + 3 = 987
1234 x 8 + 4 = 9876
12345 x 8 + 5 = 98765
123456 x 8 + 6 = 987654
1234567 x 8 + 7 = 9876543
12345678 x 8 + 8 = 98765432
123456789 x 8 + 9 = 987654321

1 x 9 + 2 = 11
12 x 9 + 3 = 111
123 x 9 + 4 = 1111
1234 x 9 + 5 = 11111
12345 x 9 + 6 = 111111
123456 x 9 + 7 = 1111111
1234567 x 9 + 8 = 11111111
12345678 x 9 + 9 = 111111111
123456789 x 9 +10= 1111111111

9 x 9 + 7 = 88
98 x 9 + 6 = 888
987 x 9 + 5 = 8888
9876 x 9 + 4 = 88888
98765 x 9 + 3 = 888888
987654 x 9 + 2 = 8888888
9876543 x 9 + 1 = 88888888
98765432 x 9 + 0 = 888888888

Brilliant, isn't it?

crated by Girmay Reda
And look at this symmetry:

1 x 1 = 1
11 x 11 = 121
111 x 111 = 12321
1111 x 1111 = 1234321
11111 x 11111 = 123454321
111111 x 111111 = 12345654321
1111111 x 1111111 = 1234567654321
11111111 x 11111111 = 123456787654321
111111111 x 111111111 = 12345678987654321
Now, take a look at this...
101%
From a strictly mathematical viewpoint:
What Equals 100%?
What does it mean to give MORE than 100%?
Ever wonder about those people who say they are giving more than 100%?
We have all been in situations where someone wants you to
GIVE OVER 100%.
How about ACHIEVING 101%?
What equals 100% in life?
Here's a little mathematical formula that might help
answer these questions:
If:
A B C D E F G H I J K L M N O P Q R S T U V W X Y Z
Is represented as:
1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26.
If:
H-A-R-D-W-O- R- K

8+1+18+4+23+ 15+18+11 = 98%
And:
K-N-O-W-L-E- D-G-E

11+14+15+23+ 12+5+4+7+ 5 = 96%
But:
A-T-T-I-T-U- D-E

1+20+20+9+20+ 21+4+5 = 100%
THEN, look how far the love of God will take you:
L-O-V-E-O-F- G-O-D

12+15+22+5+15+ 6+7+15+4 = 101%
Therefore, one can conclude with mathematical certainty that:
While Hard Work and Knowledge will get you close, and Attitude will
get you there, It's the Love of God that will put you over the top!
It's up to you if you share this with your friends & loved ones just
the way I did..
Have a nice day & God bless!!



ከባራክ ኦባማ....

ሞቱን በሰማሁ ጊዜ አባቴ ለእኔ ተረት ሆነብኝ፡፡ ከሰው ያነሰም የበለጠም ተረት፡፡ በ1963 ከሃዋይ ስወጣ ገና የሁለት ዓመት ህፃን ነበርኩ፤ ስለዚህም እሱን የማውቀው እናቴና አያቶቼ በሚነግሩኝ ታሪኮች ውስጥ ነው፡፡


የራሴን ትዝታዎች መሰብሰብ በጀመርኩበት ዕድሜዬ ላይ እናቴ ከሌላ ሰው ጋር ግንኙነት ጀምራለች፡፡ ነጭና ጥቁር ፎቶዎቹ ለምን ርቀው እንደተቀመጡም ገብቶኛል፡፡ አንዳንዴ ፎቶዎቹ ላይ የሚያስቀውን ፊቱን፣ ግንባሩንና ከዕድሜው በላይ ሽማግሌ የሚያስመስለውን ወፍራም መነፅሩን እመለከታለሁ፤ የህይወት ጉዞው በአንድ ትረካ ተቋጥሮ ሲቀርብልኝም በፅሞና አዳምጣለሁ፡፡

አፍሪካዊ ነበር - አሌጐ በተባለ መንደር ከሉዎ ጐሳ የተገኘ ኬንያዊ፡፡ መንደሩ የደሃ መንደር ነበር፡፡ አባቱንና የእኔ አያት የሆኑት ሁሴን ኦንያንጐ ኦባማ ታዋቂ ገበሬ፣ የጐሳው ሽማግሌ እንዲሁም የመፈወስ ስልጣን የተሰጣቸው ባለመድሃኒት (ሐኪም) ነበሩ፡፡ አባቴ ያደገው የአባቱን ፍየሎች እየጠበቀ፣ ኋላም የእንግሊዝ ቅኝ አገዛዝ አስተዳደር ባቋቋመው ትምህርት ቤት እየተማረ ነው፡፡ የአባቴ እምቅ ብቃት የተስፋ ጭላንጭል ያሳየው እዚህ ትምህርት ቤት ነው፡፡ በኋላ ናይሮቢ መማር የሚያስችል የትምህርት ዕድል አግኝቷል፤ ቀጥሎ በኬንያ የነፃነት ዋዜማ በኬንያ መሪዎችና በአሜሪካውያን ስፖንሰሮች ተመርጦ፤ የምዕራባውያንን ቴክኖሎጂ ቀስመው አዲሲቱን አፍሪካ ለመመስረት ይረዳሉ ከተባሉ የአፍሪካ ልጆች አንዱ በመሆን ለትምህርት ወደ አሜሪካ ተላከ፡፡

በ1959፣ በሃያ ሦስት ዓመቱ የተቋሙ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ተማሪ ሆኖ ሃዋይ ዩኒቨርሲቲ ደረሰ፡፡ ኢኮኖሚትሪክስ አጥንቶ በሦስተኛው ዓመት ከክፍል ጓደኞቹ አንደኛ ሆኖ ትምህርቱን አጠናቀቀ፡፡ ቁጥር ስፍር የሌላቸው ጓደኞች ነበሩት፤ ዓለም አቀፍ የተማሪዎች ማህበር እንዲመሰረት ከመርዳቱ በላይ የማህበሩ የመጀመያው ፕሬዚዳንትም ሆኗል፡፡ የሩሲያኛ ቋንቋ የሚማርበት ክፍል ውስጥ ከአንዲት የአሥራ ስምንት ዓመት ዓይናፋር አሜሪካዊት ልጃገረድ ጋር ተዋወቀ፤ ተፋቀሩ፡፡ የልጃገረዷ ቤተሰቦች መጀመሪያ ባይደሰቱም የኋላ ኋላ በጨዋታ አዋቂነቱና በምሁርነቱ ተረቱ፤ እናም ወጣቶቹ ጥንዶች ተጋቡ፤ እሷም ለስሙ መጠሪያ የሚሆን ወንድ ልጅ ወለደችለት፡፡ ይሄኔ ሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ዶክትሬት ዲግሪውን የሚቀጥልበትን ዕድል አሸነፈ፤ ቤተሰቡን ወደዚያ የሚያዛውርበት ገንዘብ ስላልነበረው ግን መለያየት መጣ፤ እሱም ለአፍሪካ የገባውን ቃል ለመፈፀም ወደ አፍሪካ ተመለሰ፡፡ እናትና ልጅ ባሉበት ቀሩ፤ የፍቅር ትስስሩ ግን በርቀት ሳይገደብ ከረመ፡፡

(አደብቴ፣ የለውጥና የታላቅነት ምስጢር (ትርጉም"፣ 2001)


የአሜሪካ አገር ስራዎችና ስሞቻቸው፡፡
Today at 4:02am
የአሜሪካ አገር ስራዎችና ስሞቻቸው፡፡
አሜሪካ አገር ስራ ክቡር ነው፡፡ ስራ ክቡር ብቻ ሳይሆን ስራ ያስከብራል፡፡ በዲስከቨሪ ቻናል Discovery Channel ደርቲ ጆብ (Dirty Jobs) የሚለውን ብታዩ ደግሞ ሰወች ምን እንደሚሰሩ ማመን ያቅታል፡፡ የኢትዮጵያውያን የስራ ምርጫ ደግሞ አይጣል ነው፡፡ በቃ መስራት የምንፈልገው ስሙ ደስ የሚለውን ብቻ ነው፡፡ አንድ ሰው አሜሪካ ሲመጣ አንዳነድ ስራዎችን መስራት በቃ ቅር እያለው፣ እዬቀፈፈው ነው፡፡ ስሙ ብቻ ለሰሚ ደስ ስለማይል በቃ ትንሽ ፈራ ተባ እያለ እራሱን ዝቅ እያደረገ መስሎት ነው የሚሰራው፡፡ ግን ስራ ክቡር መሆኑን ሲያውቅ በራሱ ይስቃል፡፡ ለምሳሌ በአማርኛ ስማቸው ከበድ የሚሉት ስራዎች ውስጥ ጥቂቶች ዘበኛ፣ ጫኝና አውራጅ፣ ፅዳት፣ ተላላኪ፣ ልጅ ጠባቂ፣ ደላላ፣ እረኛ፣ ዳቦ ጋጋሪ፣ እስተናጋጅ፣ አልጋ እንጣፊ፣ ስሃን አጣቢ፣ ወጥ ቤት፣ ሊስትረሮ፣ ሱቅ በደረቴ፣ ቢራ ቀጂ፣ የእድር ጡርንባ ነፊ፣ እሬሳ ገኛዥ፣ ቁራሌ፣ ወያላ፣ ግንበኛ፣ አቃጣሪ፣ ልብስ አጣቢ፣ መኪና አጣቢ፣ ልኳንዳ ቤት፣ ሌላለም ልላም ስም ሰለምንሰጠው ትንሽ ከበድ ሲሉ ግን እስኪ እነዚህን ስራዎች በእንግሊዘኛ ስንጠራቸውን እንዴት አድርገው እንደሚጣፍጡ እንመልከት
ዘበኛ፣ Security officer, private guard
ጫኝና አውራጅ፣ Luggage handler, check in specialist,
ፅዳት፣ Maintenance,
ተላላኪ፣ Messenger፣ delivery
ልጅ ጠባቂ፣ Child Development assistant
ደላላ፣ Broker, professional adviser
እረኛ፣ Ranger
ዳቦ ጋጋሪ፣ Bakery
እስተናጋጅ፣ Customer services,
አልጋ እንጣፊ: House Keeping
ስሃን አጣቢ= dishwasher or busboy
ወጥ ቤት= cook sometimes chef
ሊስትረሮ= VIP services specialist
ሱቅ በደረቴ፣ Gift Shop
ቢራ ቀጂ፣ bartender, barrista
የእድር ጡርንባ ነፊ፣ Announcer
ወያላ= conductor
ቁራሌ = mobile maintenance
ግንበኛ = general contractor
ልብስ አጣቢ= dry cleaning
አቃጣሪ = dating service
መኪና አጣቢ፣ Detail service
ልኳንዳ ቤት፣ Meat Department Specialist

ይህንን እና ሌሞችንም ሰራዎች በአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡ እንደሚመስለኝ የአንዳንዶቻችን ችግር ከስሙ ስለሆን ስራውን በስራነቱ ካመንበት የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው ነውና ምንም በሉት ምንም ዋናው ስራን ማክበር ሰለሆነ በስራችሁ ኩሩ፡፡
ለምሳሌ እኔ ድሮ ሳውቀው በቆሎ ጠብሰው የሚሸጡ ሰወች ነበሩ፣ ከዚህ አገር አንዳነድ በዕላት ላይ በቆሎ ተጠብሶ ሲሸጥ አያለሁ፣ ያውም አንዷን በቆሎ በ 5 ዶላር፡፡ አሁን ይህንን ስራ የሚሰራ አበሻ ምን እሰራለሁ በሎ ይናገራል፡፡ ይታያችሁ ስልክ ሲደውል እኔ በቆሎ እዬጠብስሁ እሸጣለሁ ቢል የቤተሰቡቹ መልስ፡፡ አይ አለማዎቅ..
በሉ ስራን አትናቁ፡፡ ስራ ክቡር ነው

ተአምረ ማርያም በግብፅ

ተአምረ ማርያም በግብፅ

ትርጉም ደረጀ መኰንን

አንፀባራቂውና ብርሃናማው የእመቤታችን መገለጥ በዋራቅ ከተማ በጊዛ ወረዳ በስሟ በተሰራው ቤተ ክርስቲያን ጉልላት ለይ

Egyptt.JPG
ባለፈው ታኅሣሥ ወር በግብጽ ጊዛ ወረዳ በዋራቅ አልሃዳር ከተማ ውስጥ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በስሟ በተሰየመው ቤተክርስቲያን ጉልላት ላይ መጀመሪያ በብርሃናዊ አካል በተገለጠች ጊዜ የታየችው በዚህ ሁኔታ ነበር

Egyptt1.JPG
ባለፈው ታኅሣሥ ወር 2002 ዓ.ም /December, 2009/ በግብፅ ካይሮ አልዘይቱን ከተማ ዋራቅ አልሀዳር በሚባል አካባቢ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በስሟ በተሠራው ቤተ ክርስቲያን በግልጽ ለሕዝብ መታየቷን፤ እንዲሁም የግብፅ ኮፕት ኦርቶዶስክ ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችንን በገሃድ መታየት እውነተኛነት ማረጋገጧን፤ በ«ሐመር» መጽሔት 17ኛ ዓመት ቁጥር 7፣ ጥር 2002 ዓ.ም እና በ«ስምዐ ጽድቅ» ጋዜጣ 17ኛ ዓመት ቁጥር 8፣ ከጥር 1 - 15 ቀን 2002 ዓ.ም እትሞቻችን በዜና መልክ ማቅረባችን ይታወቃል፡፡

ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በገሃድ መገለጥ በግብፅ የሚገኙ እና ሌሎችም ታላላቅ ዓለም አቀፍ ብዙኃን መገናኛ በስፋት ዘግበውታል፡፡ ይህንኑ የእመቤታችንን ተአምር በሰፊው ከዘገቡት ጋዜጦች መካከል በግብፅ ካይሮ እየታተመ የሚሠራጨው «ዋታኒ» /WATANI International/ ጋዜጣ አንዱ ነው፡፡ ለውድ አንባቢዎቻችን ሰፊ ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ «ዋታኒ» /WATANI/ ጋዜጣ በእሑድ ታኅሣሥ 11 ቀን 2002 ዓ.ም /20, December 2009, 11 Kyahk 1726, 3Moharram 1431, YEAR9 ISSUE 462/ እትሙ የዘገበውን ተርጉመን አቅርበነዋል፡፡

ከጊዛ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሀገረ ስብከት የተሰጠ መግለጫ
በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳይ ዘመን እና በጊዛው ሊቀ ጳጳስ አባ ዱማዲዮስ

የጊዛ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጽ/ቤት በታኅሣሥ ወር በዕለተ ዓርብ ታኅሣሥ 2 ቀን 2002 ዓ.ም /Friday 11, December 2009/ ልክ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ላይ በጊዛ ወረዳ በዋራቅ አል- ሃዳር ከተማ ውስጥ በምትገኘው በስሟ በተሰየመው ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ድንግል ማርያም በሙሉ ግርማ ሞገሷ መታየቷን ገለፀ፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም በሙሉ ቁመናዋ፣ የሚያንፀባርቅ መጎናፀፊያዋን ደርባ ፀአዳ የብርሃን ልብሷን ለብሳና ደማቅ ሰማያዊ ሰበኗን ታጥቃ የብርሃን አክሊል እንደደፋች በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉልላት አናት ላይ ረብባ ታይታለች፡፡ እመቤታችን የብርሃን አክሊልም በጭንቅላቷ ደፍታ ነበር፡፡ በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉልላት ላይ የሚገኙት መስቀሎችም ላይ አንፀባራቂ ብርሃን ይታይ ነበር፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በቤተ ክርስቲያኑ ጉልላቶች መካከልና በበሮቹ አናት ላይ በሚገኙት ሁለት ማማዎች መካከልም ስትዘዋወር የአካባቢው ነዋሪዎች በሙሉ አንዳቸውም ሳይቀሩ አይተዋታል፡፡

የእመቤታችን መገለጥ አርብ ሌሊት ከሰባት ሰዓት እስከ አሥር ሰዓት ድረስ የዘለቀ ሲሆን ምስሏም በፎቶ ካሜራና በተንቀሳቃሽ ስልክ ካሜራ ተቀርጿል፡፡ ወደ ሦስት ሺሕ የሚጠጉ የአካባቢው ነዋሪዎች ከአጎራባች ቀበሌዎች የመጡና ተላላፊ መንገደኞች በሙሉ በቤተ ክርስቲያኗ ዐውደ ምሕረትና ዙሪያ እንዲሁም በአቅራቢያው ጎዳና ላይ ተሰባስበው የእመቤታችንን በገሃድ መገለጥ በዓይናቸው አይተዋል፡፡

ከዕለተ ዓርብ /አመሻሹ ጀምሮ፣ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዙሪያ የተከማቸው ምእመን /ሕዝብ/፣ ከምሽቱ በተለያዩ ጊዜያት ከቤተ ክርስቲያቱ አናት ላይ አንፀባራቂ ፀአዳ ርግቦች ከፍ ብለው ሲበሩ ያዩ ሲሆን በተጨማሪም ከገነት /ከሰማየ ሰማያት/ ከዋክብት በድንገት ተፈንጥቀው በመውጣት በአካባቢው እስከ ሁለት መቶ ሜትር ድረስ ሲወረወሩና ተመልሰው በድንገት ሲሰወሩ አስተውለዋል፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ ዙሪያ የተሰባሰበው ሕዝብ ለቅድስት ድንግል ማርያም መዝሙርና ምስጋና ያለማቋረጥ አቅርበዋል፡፡

ይህ ለቤተ ክርስቲያኗ እና ለመላው የግብጽ ሕዝብ ታላቅ ቡራኬ ነው፡፡ በረከቷና ምልጃዋ ሁላችንንም ይራዳን አሜን፡፡
ፊርማ
አባ ቴዎዶሲዎስ
የጊዛ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ቪክቶር ሰላማ
ናዲር ሹክሪ

በወርሃ ታኅሣሥ ዕለተ ሐሙስ /ለአርብ አጥቢያ/ ጥር 2 ቀን 2002 ዓ.ም /11th, December 2009/ ከዕኩለ ሌሊት አለፍ ብሎ በሀገረ ግብፅ በጊዛ ወረዳ በሰዎች በተጨናነቀችዋ ዋራቅ አል ሃዳር ከተማ በምትገኘዋ የቅድስት ድንግል እና የመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ጣራና ጉልላት ላይ እንግዳ የሆነ ሰማያዊ ብርሃን ሲያንዣብብ በዕለቱ ተረኛ የነበሩ የቤተ ክርስቲያኒቷ ዘቦች ተመለከቱ፡፡

የአካባቢውን የመንገድ መብራት የዋጠው አንፀባራቂው ደማቅ ብርሃን በአካባቢው በሚገኝ ካፊቴሪያ እጅብ ብለው እየተዝናኑ የነበሩትን ሙስሊሞችንም ጭምር ትኩረት ማርኮ ነበር፡፡ በክስተቱ የተደመሙት እኒሁ ሙስሊሞች ደማቁ ብርሃን እየተሰበሰበ ወደ አንድ የሴት አካል ቅርፅ ሲቀየር አስተዋሉ፡፡ በአካባቢው ጎዳና በመጓዝ ላይ የነበሩ ጥቂት አማንያን ክርስቲያኖችም የሚያዩት ብርሃን የተወዳጇ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ውብ ምስል መሆኑ ወዲያውኑ ለመለየት ችለዋል፡፡ እመቤታችን ከራስ ፀጉሯ እስከ እግር ጥፍሯ ድረስ ብርሃን ለብሳ ብርሃን ተጎናጽፋ ወርቃማ አክሊሏን እንደደፋች ረዥም አብረቅራቂ ነጭ የብርሃን ቀሚሷንና ባለሰማያዊ ደማቅ መጎናፀፊያዋን ደርባ በቤተ ክርስቲያኑ ጉልላት አናት ላይ በሙሉ ቁመናዋ ተገልፃ ታየች፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ አናት ላይ እና በሁለቱ የቤተ ክርስቲያኗ ማማዎች መካከል ረብባ ስታንዣብብ የጉልላቶቹ መስቀሎች ብርሃን ማመንጨት ጀመሩ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ሁኔታ ዓርብ ከለሌቱ ሰባት ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ አስር ሰዓት ድረስ በስሟ በተሠራው ቤተክርስቲያን አናት ላይ እየተዘዋወረች ተገልጣ ታይታለች፡፡

የመገለጧ ዜና በከተማዋ ተሠራጨ፡፡ ሞባይል ስልክ በመጠቀም ጓደኛሞች መጠራራት ጀመሩ፡፡ ከፊሎቹ ይህን ትንግርት በቪዲዮ ካሜራ በመቅረፅ ለወዳጅ ዘመድ መላኩን ተያያዙት፡፡ ቀስ በቀስ የቤተ ክርስቲያኗ ዙሪያ በሰዎች ጎርፍ ተጥለቀለቀ፡፡ የዚያኑ ምሽት ቀደም ብለው ወደየቤታቸው የሄዱት የቤተ ክርስቲያኗ ቀሳውስት ተጠርተው የእመቤታችንን መገለጥ በዐይናቸው ለማየት በቁ፡፡ የጊዛ መስተዳድር የፖ¬ሊስና ፀጥታ ክፍል የዚህ ትንግርት ዜና እንደደረሳቸው ወደ ሥፍራው የፖሊስ ኃይል በመላክ ቤተ ክርስቲያኗን እንደ መቀነት ከበው ሲጠብቁና የታዳሚውን ደህንነት እና ሥነ ሥርዓት ሲያስከብሩ አደሩ፡፡

የእመቤታችን መገለጥ ዜና በእንደዚህ ሁኔታ በፍጥነት በመሠራጨቱ በቀጣዮቹ ጥቂት ሰዓታት የደስታ ሲቃ በተናነቃቸውና እጅግ በተደመሙ ታዳሚዎች ሥፍራው ተሞላ፡፡

የብርሃን እናቱ /እሙ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ/

የሚደንቀው ነገር የእመቤታችንን መገለጥ አይተው ዜናውን ያሠራጩት የአካባቢው ሙስሊሞች ነዋሪዎች መሆናቸው ነበር፡፡ በሉቃስ ወንጌል ላይም እመቤታችን ድንግል ማርያም «... እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል፤ . . .» /ሉቃ.1-48/ ያለችው እንዲሁ እንዳልነበር ይህ ክስተት ያሳያል፡፡

ዋታኒ /WATANI International/ ሳምንታዊው የዕለተ ሰንበት ጋዜጣ የእመቤታችንን የመገለጥ ክስተት በትኩሱ ለመዘገብ ሪፖርተሮቹ በቦታው በአካል እንዲገኙ አድርጓል፡፡ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በቦታው በመገኘት ቤተ ክርስቲያኗን ከበው ነው ያደሩት፡፡ አጥንት የሚቆረጥመው የክያህክ /Kyahk/ የታኅሣሥ ወር/ ምሽት ብርድ ሳይበግራቸው ታዳሚዎቹ እስከሚቀጥለው ንጋት ድረስ ከበረከቱ ለመሳተፍ እሳት አንድደው እየሞቁ በዚያው በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ከትመው ነበር ያደሩት፡፡ የምሽቱን አየር በነበረው የደስታ ድባብ ላይ ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሚቀርበው የማያቋርጠው መዝሙርና ምሥጋና ተጨምሮ አድምቆት ነበር፡፡ የምሽቱ ድባብ ሁኔታውን የንግሥ ክብረ በዓል ሲያስመስለው በተለይ ትኩስ የሚጠጣና የሚበላ ሳንድዊች ምግብ አዝዋሪዎችም ከወዲያ ወዲህ ተፍ ተፍ እያሉ ሲያስተናግዱ ለምሽቱ ድምቀት ሰጥተውታል፡፡ የምሽቱ ተአምር ታዳሚዎች የሙስሊሞችና ክርስቲያኖች ስብስብ ነበር፡፡ ዓይነ ርግብ ያጠለቁ ሴቶች ዓይነ ርግብ ካላደረጉት ጎን ለጎን ቆመው ይታዩ ነበር፡፡ ሁሉም የእመቤታችንን መገለጥ በመደመም ይመለከቱ ነበር፡፡

ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ አንፀባራቂው ብርሃናማ የሴት ቅርፅ ያለው ምስል ከቤተ ክርስቲያኑ ጣራ ወደላይ ከፍ እያለ ከወጣ በኋላ በቤተ ክርስቲያኗ ማማና ጉልላት ላይ በድምቀት ረብቦ አረፈ፡፡ ሕዝቡ ደስታውን ከፍ ባለ ድምፅ «ድንግል ሆይ! ቅድስት ድንግል ተገለጠች!» እያለ እልልታውን ከዳር እስከ ዳር አቀለጠው፡፡ ባቅራቢያው ከሚኖሩ ጎረቤቶቻቸው መኖሪያ ቤቶች ጣሪያ ላይ በወፋፍራም ልብሶቻቸው ተጀቡነው ይህን ትንግርት ይመለከቱ የነበሩ በመቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች በጎዳናው ላይ የነበረውን ተመልካች ደስታ ለመጋራት ከሕዝቡ ጋር ተቀላቅለው በአንድነት «የብርሃን እናቱ ድንግል ሆይ ቅድስት ሆይ፣ ትጎበኝን ዘንድ ሁሌም ወደኛ ነይ ነይ፡፡» እያሉ በአንድነት ዘመሩ፡፡

በፍቅሯ ይቃጠሉና በጭንቅና መከራ ተከበው የነበሩ ግብፃውያን ሁሉ አንዳቸውም እንኳ ተስፋ እንዳይቆርጡና እንዲጽናኑ ታበረታታቸው ዘንድ እናታቸው ቅድስት ድንግል ማርያም ከነሙሉ ክብሯና ከሚያስደምም ግርማ ሞገስ ጋር እንደገና ደግማ ተገለጠችላቸው፡፡

ገበርነ ሐሴት፣

ሐማዳ ሙሐመድ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ትይዩ በምትገኘው ካፍቴሪያ ውስጥ አስተናጋጅ ነው፡፡ «ዋታኒ» ጋዜጣ አነጋግሮት ነበር፡፡ ሐማዳ እና የቤተ ክርስቲያኗ የጥበቃ ተረኞች የእመቤታችንን መገለጥ በመጀመሪያ ያዩት የዓይን ምስክሮች ናቸው፡፡ «ሐሙስ ምሽት ታኅሣሥ 2 ቀን 2002 ዓ.ም /December 10,2009/ አምሽቼ እየሠራሁ ነበር፡፡ እኔና የሥራ ባልደረቦቼ በጣም ያስገረመንን ደማቅ የብርሃን ጎርፍ ተመለከትን፣» ይላል ሐማዳ ሙሐመድ፡፡ «ከዚያም ይህ ትንግርት ምን እንደሆነ እያሰላሰልን የቤተ ክርስቲያኒቱን ተረኛ ዘቦች ቀሰቀስናቸው፡፡ ወዲያውኑ ይህ ደማቅ የብርሃን ጎርፍ ቅርፅ እየያዘ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አናት ላይ አረፈ፡፡ ይህ ብርሃን ለቅጽበት ተሰወረንና እንደገና ተገለጠ፡፡ በአጠገባችን ቆሞ የነበረ አንድ ክርስቲያን «ይህች ቅድስት ድንግል ናት!» እያለ ጮኸ፡፡ ብዙ ሰዎችም መሰባሰብ ጀመሩ፡፡ ይህን ጊዜ ሰዓቱ ከለሊቱ ወደ ዘጠኝ ሰዓት ገደማ ይሆናል፡፡ ቅድስት ድንግል እንደገና በሙሉ ቁመናዋ ነጭ ብርሃናማ ቀሚስና ደማቅና ውብ ሰማያዊ መጎናፀፊያ ደርባ ተገልጣ ታየች፡፡ በቤተ ክርስቲያኗ ጣራና ጉልላት ላይ ከወዲያ ወዲህ እየተዘዋወረች ቆየች፡፡» እንደዚሁ ከዚህ በፊት አንድ ምሽት በሚያንፀባቁ በብርሃናማ ርግቦች ተከባ መገለጧ ይታወሳል፡፡ የዛሬውን ምሽት ተኣምር ለማየት የታደለው ሐማዳ ሙሐመድ ለ«ዋታኒ» ጋዜጣ ዘጋቢ፤ የቅድስት ድንግል መገለጥ ለክርስቲያኖችና ለሙስሊሞች ታላቅ ደስታ መሆኑን ተናግሯል፡፡

ሐሰን ሙሐመድ /ሐሰን አንቦባ በመባል ይታወቃል/ የእመቤታችንን መገለጥ ካዩትና እማኝ ከሆኑት የመጀመሪያዎቹ ሰዎች መካከል አንዱ ነበር፡፡ ሐሰን የጓደኛውን ሐማዳ ቃል የሚጋራ ሲሆን በተጨማሪም በሥዕለ ድንግል ማርያም ያየው እና አሁን ተገልጣ ያያት ድንግል ማርያም ፍፁም አንድ ዓይነት እንደሆነበት መስክሯል፡፡

ሌላው የዚህ ድንቅ ምሽት ታዳሚ የነበረውና ከጓደኞቹ ጋር በዚያች ካፍቴሪያ ቁጭ ብሎ ሲስተናገድ የነበረው ኡሰማ አቡ ሐዲድ የደስታ ሲቃ እየፈነቀለው፤ «የቅድስት ድንግልን ምስል በተንቀሳቃሽ /ሞባይል/ ስልኬ ካሜራ አንስቻታለሁ» በማለት ለ«ዋታኒ» ጋዜጣ አስረግጦ ተናግሮአል፡፡ ኡስማ በዚሁ ሳያባቃ «ብርሃኗ ከምሽት ጨረቃ የበለጠ እጅግ ውብ ነበር» በማለት ገልጿል፡፡

ይህን ተአምር ያዩ ሙስሊሞች በሙሉ ወዲያውኑ ክርስቲያን ጎረቤቶቻቸውን በመቀስቀስ የእመቤታችንን መገለጥ ሳያመልጣቸው እንዲያዩ አድርገዋል፡፡ ሙስሊም ጎረቤቱ ቀስቅሶት የነገረው የክርስትና ሃይማኖት አማኝ የሆነው አሸራፍ አብዱል ማላክ ወደ ጎዳናው ገስግሶ ታዳሚዎችን ለመቀላቀል አፍታም አልወሰደበት፡፡ አሸራፍ ዓይኑ ያየውን እንዲህ ሲል መስክሯል፡፡ «ከደመናት መካከል ሰንጥቆ የሚወጣው ሰማያዊ ብርሃን ቅድስት ድንግልን አጅቧት ከቤተ ክርስቲያኑ መንታ ማማ መካከል በሚገኘው መስቀል ላይ እመቤታችን ስታርፍ አየሁ፡፡»

ሌላዋ ሙስሊም የዋራቅ ነዋሪ «ድንግል ማርያም በቅዱስ ቁርአናችን ላይ የተከበረችና የተወደሰች ናት፣ በሁሉም ክርስቲያኖችና ሙስሊሞች ዘንድ የተወደደች ናት» በማለት አሳቧን በደስታ ገልፃለች፡፡ አክላም «ለዚህም ነው በዋራቅ የምንገኝ ሁላችንም እጅግ የተደሰትነው፡፡» ብላለች፡፡

እርግጠኞች በሆንን ጊዜ

«ዋታኒ» ጋዜጣ የጠቅላላ ጊዛ /Giza/ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የሆኑትን አባ ቴዎዲዎስዮስን አነጋግሯቸው ነበር፡፡ የቅድስት ድንግል ማርያምን ተገልጣ መታየት የዋራቅ ቤተ ክርስቲያን ቀሳውስት በስልክ ደውለው በነገሩኝ ጊዜ ማለትም በታኅሣሥ 3 ቀን /Deceber 11,2009/ እኔ በስተደቡብ ምዕራብ አሌክሳንድሪያ በማርዮት ወረዳ በምትገኘው በማር ሚና ገዳም ውስጥ ነበርኩኝ፡፡ ቀሳውስቱን የእመቤታችን መገለጥ ትክክለኛ መሆኑን እርግጠኛ እስክንሆን ድረስ አንዳችም መግለጫ በቤተ ክርስቲያን ስም እንዳያወጡ ከማስጠንቀቂያ ጋር አጥብቄ መከርኳቸው፡፡ ምክንያቱም ያልተረጋገጠ ነገር እንዳይገለጽ ነው፡፡ ከዚያም ለሕክምና በአሜሪካ ለሚገኙት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሽኖዳ ስለጉዳዩ አሳወቅናቸው፡፡ ቅዱስነታቸውም ካሉበት ቦታ ሆነው ሁኔታውን ከኛ ጋር በትኩረት መከታተል ጀመሩ፡፡ በመጨረሻም፣ የቅድስት ድንግል ማርያም መገለጥ ትክክለኛ መሆኑ ሲረጋገጥና፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችም መገለጧን እንዳዩ እርግጠኞች በሆንን ጊዜ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቤተ ክርስቲያኗ መልእክት ታትሞ እንዲሠራጭ አደረግን፡፡

በጣም በሚያስደንቅ ሁኔታ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል መገለጥ በዋራቅ ወረዳ እንደተከሰተው ዓይነት ሁሉ በካይሮና በጊዛ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች ያልተለመደ ብርሃንና በዛ ያሉ ርግቦች መታየታቸውን ነዋሪዎቹ እማኝነታቸውን መስጠታቸው ተዘግቧል፡፡

ጥርጣሬ

እዛው የሚያገለግሉ አባ ቢሻይ እንደሚሉት፤ በዋራቅ ወረዳ የምትገኘው ቤተ ክርስቲያን የተቆረቆረችው አንድ በእግዚአብሔር ተጠርቶ ይኼን ዓለም ትቶ በመነነ ክርስቲያን በተለገሠች ቁራጭ መሬት ላይ ነበር፡፡ ከዚያ በፊት ግን በዚህ ወረዳ የሚኖሩ ክርስቲያን ምእምናን ከአንዲት ፍርስራሽ ካታኰምብ /ዋሻ/ በስተቀር በውኑ ጸሎት የሚያደርሱበት ቦታ እንኳ አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም ግን በ2000 እ.ኤ.አ ቤተ ክርስቲያኗ ከሚመለከተው የአስተዳደር አካል የግንባታ ፍቃድ አገኘች፡፡ አሁን የምትገኘውን ቤተ ክርስቲያን በ750 ካሬ ሜትር ላይ ሰባ ቀን ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ግንባታዋ ከተጠናቀቀ በኋላ በቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ ሣልሣይ ተመርቆ በአሁኑ ጊዜ ከሦስት ሺሕ ምእመናን በላይ እየተገለገሉባት ትገኛለች፡፡

ማሐር ናዝሚ ስለእመቤታችን መገለጥ የተለየ መንፈሳዊ እይታ አለው፡፡ «እግዚአብሔር እኛ የዋራቅ ወረዳ ምእመናንን ወደራሱ ያቀርበን ዘንድ ፈቅዶናል፡፡ አብዛኞቻችን ነጋዴዎች ወይም የአነስተኛ ፋብሪካ ሠራተኞች እንደመሆናችን ለእርሱ የምንሰጠው አንዳችም ጊዜ አልነበረንም፡፡ በቃ የዕለት ጉርሳችንን ለማሟላት ስንባክን ነው የምንውለው፡፡ ከእመቤታችን ድንግል ማርያም መገለጥ በኋላ ግን፤ ቤተ ክርስቲያኒቱ በአማኞች መጥለቅለቅ ጀምራለች»፡፡ በማለት ተናግሯል፡፡

የዋራቅ ቤተ ክርስቲያን ቄስ የሆኑት አባ ዳውድ ኢብራሂም ለ«ዋታኒ» ጋዜጣ ሲያስረዱ፤ «የእመቤታችን መገለጥ የሰላም መልእክትና የእርቅ ጥሪ ነው» ብለውታል፡፡

«የእመቤታችንን መገለጥ ዜና እንደሰማን ወዲያውኑ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጉዳዩን አሳወቅን» ይላሉ አባ ዳውድ፡፡ «ሊቀ ጳጳሱም በተራቸው ዜናውን በሰሜን አሜሪካ /USA/ በሕክምና ላይ ለሚገኙት ለቅዱስነታቸው አቡነ ሺኖዳ አበሰሯቸው» አባ ዳውድ አክለውም፤ «ቤተ ክርስቲያኒቱ የተከሰተውን የእመቤታችንን መገለጥ ሁኔታ የዓይን እማኞችን ምስክርነት፣ የፎቶ ግራፍና የቪዲዮ ምስል መረጃዎችን ጨምሮ በጥንቃቄ መዝግባና መረጃ አጠናቅራ አጠናቃለች፡፡

እንዲህ ያለው ክስተት ተጠራጣሪዎችን የሚያበሳጭ ወይም ስሜታቸውን የሚያስቆጣ እንደሚሆን ይታወቃል፡፡ በተለይ የብዙኃን መገናኛ አውታሮች በሙሉ ሁኔታውን አለማመን ወይም ላለማመን መፈለጋቸውን አሳይተዋል፡፡ ይህም ሆኖ ግን፤ «ክርስቲያኖች እምነታቸውን ለማረጋገጥ የግድ የቅድስት ድንግል ማርያም መገለጥ ወይም ተአምራዊ መከሰት አያስፈልጋቸውም፤ ምክንያቱም እነሱ ቀድሞውኑ እምነታቸው የተመሠረተው በማይናወጸው አለት ላይ በመሆኑ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያላቸው እምነት እጅግ የጸና ነው፡፡» ብለዋል አባ ዳውድ፡፡ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃና በረከት አይለየን አሜን፡፡


ወስብሐት ለእግዚአብሔር

በጠበል ከሆዷ ውስጥ ከስምንት በላይ ነፍሳት የወጡላት ወጣት

በይብረሁ ይጥና

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በጠበል አማካኝነት ተአምራት የተደረገላቸው ብዙ የሰው ልጅ ታሪኮችን እናገኛለን፡፡ ከነዚህ መካከል አንዱ የሶርያው ንጉሥ ሠራዊት አለቃ የነበረው ንዕማን ለጌታው የቅርብ ሰውና የተከበረ ሲሆን ነገር ግን በለምጽ የተመታ ሰው ነበር፡፡

Emebate.JPGEmebate1.JPG

ወጣት እመቤት ሥራው ብዙ ወጣት እመቤት ጠበሉን ከጠጣች በኋላ

ከሆዷ ውስጥ ከወጡላት ነፍሳት አንደኛው

እግዚአብሔርም ሰው ኤልሳዕ «ሂድ በዮርዳኖስም ሰባት ጊዜ ታጠብ፣ ሥጋህም ይፈወሳል» አለው፡፡ «የእግዚአብሔር ሰው እንደተናገረው በዮርዳኖስ ሰባት ጊዜ ብቅ ጥልቅ አለ፤ ሥጋውም እንደገና እንደ ትንሽ ብላቴና ሥጋ ሆኖ ተመለሰ ንጹሕም ሆነ» ይላል /2ነገ.5-14/፡፡ እንደዚሁም ለአሥራ ሁለት ዓመት ያህል ያለ ማቋረጥ ደም ይፈሳት የነበረችውን ሴት እግዚአብሔር እንዳነፃት በማቴዎስ ወንጌል 10-20 ላይ እንመለከታለን፡፡ ይህም የልብሱን ጫፍ ነክቼ «እድናለሁ» አለች፡፡ ኢየሱስም «ልጄ ሆይ አይዞሽ እምነትሽ አድኖሻል» አላት፡፡ ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች ይላል፡፡

ልክ እንደዚህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ ሁሉ የእግዚአብሔር ድንቅ ተአምራት የተደረገላቸውና በጠበል የተፈወሱ ሰዎች ብዙዎች ናቸው፡፡ በዛሬም ጽሑፋችን የምንመለከተው በእግዚአብሔር ቸርነት በጠበል ተፈውሳ ከሆዷ ውስጥ ከስምንት ዓይነት በላይ ነፍሳት የወጡላትን ወጣት ይሆናል፡፡
እባብ፣ አይጥ፣ እንቁራሪት፣ እንሽላሊት፣ ሸረሪት፣ ኣባ ጨጓሬ፣ ቀንድ አውጣ፣ አልቅት፣ ጢንዚዛና ሌሎችም ምንነታቸው የማይታወቁ ነፍሳት ከሰው ልጅ ሆድ ውስጥ ወጡ ቢባል ማን ያምን ይሆን? ተሸካሚውስ ሰው እንዴት በሕይወት ሊቆይ ይችላል? የሚሉትን ሁሉ እንደ ሰው ሰውኛ ስናስብ ፈጽሞ ሊታመን የማይችል ነገር ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሁኔታው /ድርጊቱ/ ከሰው ሕሊና ውጪ በመሆኑ ማንም ሰው በቀላሉ ሊቀበለው ስለማይችል ነው፡፡

ነገር ግን ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና እውነት ሆኖ ተገኘ፡፡ የወጣቷ ቤተሰቦች፣ ጎረቤትና አጥማቂዎች በዐይናቸው አይተው አረጋግጠዋል፡፡ እኛ እግዚአብሔር በኪነ ጥበቡ ድንቅ ተአምሩን ያደረገላትን ጨምሮ እሷን ሲያስታምሙ፣ ሲያስጠምቁ የነበሩ ቤተሰቦችና ጎረቤት እንዲሁም ሲያጠምቋት የነበሩ አባቶችን በማነጋገር እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡ በቅድሚያ ግን ከባለጉዳዩ የሚበልጥ የለምና በጠበል የተፈወሰችውን ወጣት እናስቀድማለን፡፡

ወጣቷ እመቤት ሥራው ብዙ ትባላለች፡፡ ተወልዳ ያደገችው በምሥራቅ ጎጃም ብቸና ከተማ ውስጥ ነው፡፡ ቤተሰቦቿ የሚተዳደሩት በግብርና ሥራ በመሆኑ የተሻለ ሥራ ለመፈለግ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ታገለግላለች፡፡ ከምትሠራባቸውም ቦታዎች አንዱ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ቡልቡላ የሚገኘው የወ/ት ወይንሸት ወልደ ሰንበት ቤት ነው፡፡ እኛም ያነጋገርናት ወደዚሁ ቤት ሄደን ነው፡፡ ምክንያቱም አንደኛ እግዚአብሔር ያደረገላትን ድንቅ ተአምር ለምእመናን ለማሳወቅ ሲሆን ሁለተኛ በአሁኑ ዘመን አንዳንድ ሰዎች ለቤት ሠራተኞቻቸው ልዩ ትኩረት በማይሰጡበት ሰዓት እሷን ግን አሠሪዎቿ እንደ ልጃቸው አድርገው እስከ መጨረሻው ድረስ በማስታመም አድነው እያስተማሯት መሆኑንም ጭምር ለማሳየት ነው፡፡ ይህ ደግሞ እግዚአብሔር የሚያዘውንና መደረግ የሚገባውን መልካም ሥራ እየሠሩ መሆኑን ለሌላው ያስተምራል ብለን ስለ አሰብን ነው፡፡

ለወጣት እመቤት ሥራው ብዙ በቅድሚያ ያነሣንላት ጥያቄ ሕመሙ የጀመረሽ መቼና እንዴት ነው? የሚል ነበር፤ እንዲህ ስትል መልሳለች፡፡ «ሕመሙ የጀመረኝ ገና የሰባት ዓመት ልጅ እያለሁ ሲሆን ከዚያን ጊዜ ጀምሮ አሁን ድረስ የማያቋርጥ ከፍተኛ የራስ ምታት ያመኝ ነበር፡፡ ይበልጥ የባሰብኝ ግን በ2001 ዓ.ም በየካቲት ወር መጨረሻ ሲሆን ለአራት ወር ያህል በተከታታይ ሐኪም ቤት ስመላለስ የማኅጸን ዕጢ ነው አሉኝ፡፡ እንዲሁም እግሬ ደህና ነበር እሱንም አመመኝ፡፡ ውስጡን እየቆረጠመ ያስነክሰኛል፡፡ ከሁሉ የባሰብኝ ሕመም ማኅፀኔን ስለነበር ብዙ ጊዜ አመላልሶኛል፡፡ በሐኪሞች በማኅፀኔ ውስጥ ዕጢ ነው ተብሎ ኦፕሬሽን ትሆኛለሽ አሉኝ፤ በተባለው ጊዜ ሄጄ ስታይ «ኢንፌክሽን /Infection/ ሆኖ ከፍተኛ ደም ስለፈሰሰ አሁን ኦፕሬሽን መሆን አትችይም» ተባልኩ፡፡ በዚያ ፈንታ ሰባት መርፌ ታዞልኝ ሕክምናውን ተከታትየ ነበር አለች፡፡

እመቤት የታዘዘላትን ሰባት መርፌ ተከታትላ ብትወጋውም ሕመሙ ሳምንት ሳይቆይ ተነሣባት፡፡ እንደቀድሞው ደም መፍሰስ ጀመረ፡፡ «ከዚህ በኋላ ቃልቲ አካባቢ አዲስ የተሠራችው ቁስቋም ጠበል ሄድኩ፡፡ ትላለች እመቤት፤ «እዚያም ሄጄ ለዐሥር ቀን ያህል ደም ከፈሰሰ በኋላ ሲቆምልኝ ጠበል መጠመቅና መጠጣት ጀመርኩ፡፡ ወደ ጠበል ቦታው የሄድኩት ግንቦት 1 ቀን 2001 ዓ.ም ሲሆን ለአንድ ወር ያህል ስጠመቅ ሁለት እንቁራሪት በትውከት ወጣልኝ፡፡ ከዚህ በኋላ ዳንኩ፤ ሌላ ችግር አይገጥመኝም ብዬ ወደ ምሠራበት ቤት ተመልሼ መጣሁ» በማለት ታሪኳን ትቀጥላለች፡፡

እመቤት ከሕመሜ ድኛለሁ ብላ ወደ ቤቷ ከመጣች በኋላ እንደገና አመመኝ አለችን፡፡ ደግሞ ሌላ ምን ነገር ገጥሟት ይሆን? መልሷን ለመስማት ቸኮልን፡፡ የነገረችን ነገር እጅግ በጣም የሚከብድና የሚዘገንን ነገር ነው፡፡ በራሷ አንደበት እንዲህ ትገልጸዋለች፡፡ «እንደገና አመመኝና ሐምሌ 5 ቀን ለ6 የቁስቋም ዋዜማ 2001 ዓ.ም ወ/ት ወይንሸት በታክሲ ወደ ጠበሉ ወሰደችኝ፡፡ ጠበሉን ጠጣሁ፤ ተጠመቅሁ ልክ የቁስቋም በዓል ዕለት ሁለት እባብ ከሆዴ ወጣልኝ፡፡ ለአራት ቀን ሙሉ ጉሮሮዬን አንቆ ይዞ ያስጨንቀኝ ነበር፡፡ እንቅልፍ የሚባል አላይም፤ ሲወጣልኝ ራሴን አላመንኩም፡፡ በድንጋጤ ራሴን አላውቅም ነበር፡፡ አንዱ በትውከት መልክ ሲወጣ ሁለተኛው እንደ ልጅ በማኅፀኔ ወጣ፡፡ ሁለቱም ነፍስ አላቸው፡፡ የወጡልኝ አውላላ ሜዳ ላይ በመሆኑ ከብት የሚጠብቁት ሊገድሉት ሲሯሯጡ በድንጋይና በድንጋይ መሐል ገብቶ አመለጣቸው፡፡ አሁንም ፈተናዬን ጨረስኩ ብዬ ወደ ቤቴ ተመለስኩ፤ ብዙም አልተሻለኝም፡፡ መጨረሻውን ማየት አለብኝ ብዬ በድጋሚ ወደ ጠበሉ ሄጄ ስጠመቅ ሐምሌ 19 ቀን የቅዱስ ገብርኤል ዕለት ሁለት ትናንሽ እባቦች ወጡልኝ፡፡ ጠበሉን ተጠምቄ ከወጣሁ በኋላ ነው ሁለቱም በትውከት ከሆዴ የወጡልኝ፡፡ ሊጠመቁ የመጡና አጥማቂዎች ያዩት ሲሆን ቤተሰቦችሽ ማየት አለባቸው ብለውኝ በዕቃ አድርጌ ወደ ቤት በማምጣት ጎረቤት ሳይቀር አይተውታል» ስትል የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ተናግራለች፡፡

በአጠቃላይ በቃልቲ ቁስቋም ለሁለት ወር ያህል እየተጠመቀች ቆይታ ከሁለት ወር በኋላ ግን በዚያው መቀጠል አልቻለችም፡፡ ምክንያቱም ደግሞ በመሐል «የአተት /የአጣዳፊ ተቅማጥና ትውከት/ በሽታ ገብቷል» ተብሎ ጠበሉ ሲዘጋ ቦሌ ቡልቡላ መድኃኔዓለምና አባ ሳሙኤል ጠበል መጀመሯን አስረድታለች፡፡ በዚያም ስትጠመቅ በየቀኑ ብዛት ያላቸው አባ ጨጓሬ እንደወጡላት ታስረዳለች፡፡ «የሚወጣልኝ ነገር ሁሉ አላልቅ ብሎ ከእኔም አልፎ ያለሁባቸውን ሰዎች እያስደነቀ መጨረሻውን ይናፍቁ ነበር፡፡ ቶሎ ቢያልቅልኝ ብዬ በአቅራቢያው እዚያው ቦሌ ቡልቡላ በሚገኘው የተክለ ሃይማኖትና የእመቤታችን ጠበል ጀመርኩ፡፡ ይህ ቦታ ቅርሶች በቅርብ ጊዜ የተገኘበትና ጠበል የፈለቀበት ነው፡፡ በዚህ ቦታ ምንነቱን የማላውቀው ነገር ወጣልኝ፡፡ ትልልቅና መልኩ ጥቁር ሲሆን የወጣልኝ ደግሞ ወደ ገደል አካባቢ አስሩጦ ከወሰደኝ በኋላ ነው፡፡ በዚያን ዕለት በተጨማሪ እንሽላሊትና ሁለት የቄብ ዶሮ እንቁላል የሚያክል ከድፍርስ ውኃ ጋር ተቀላቅሎ ወጣልኝ፡፡ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፤ አሁን ሙሉ ጤነኛ ነኝ፡፡ ራስ ምታቱም ሆነ ደም መፍሰሱ ቆሞልኛል» አለችን፡፡

ወጣት እመቤት ሥራውብዙ ንግግሯን ብትጨርስም የሕመሙ መነሻ ምን እንደነበር ጠየቅናት፡፡ «እኔ በመጀመሪያ ቃሊቲ ቁስቋም ጠበል ስጀምር አጋንንት፣ መተትና ቡዳ ነኝ ብሎ እንደጮኸ አስታማሚዎች ነግረውኛል፡፡ ከዚህ ውጭ ምንም የማውቀው ነገር የለም፡፡ የአስታመሙኝ ሰዎች ሁኔታውን ስለሚያውቁ እነሱን መጠየቅ ይቻላል፡፡ እኔን ግን እግዚአብሔር አድኖኛል፤ አመሰግነዋለሁ፡፡

በመቀጠል ለታመመ ሰው አስታማሚ ያስፈልጋልና ያስታመሙኝን አሠሪዎቼን አመስግኑልኝ፡፡ ከዚህ በፊት በስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ ወፍ የወጣላት እኅት አለች የሚለውን ወሬ ስሰማ ከዚህ የባሰ የእኔን ቢሰሙ ምን ሊሉ ነው? ብዬ የእግዚአብሔርን ቸርነት ሰው እንዲያውቀውና አስታማሚዎቼን እንድታመሰግኑልኝ በማሰብ ነው፡፡ አሠሪዎቼ ቤት እየዘጉና እየከፈቱ ምግብ አመላልሰው አስታመውኛል፡፡ ሌላ ሰው ሳይቀጥሩና የእኔን ሥራ እየሠሩ ሲያስታምሙ ማንም ዘመድ የማያደርገውን ሥራ ሠርተዋል» ብላ ከልቧ አለቀሰች፡፡ ቃላት ቢያጥራት በዕንባዋ ጭምር ከልብ የመነጨ ምስጋናዋን ገለጸች፡፡ እሷን አጽናንተን በቀጥታ ጥያቄያችንን ያስከተልነው አስታመውኛል ወደአለቻቸው አሠሪዎቿ ነው፡፡

ወ/ሪት ወይንሸት ወልደ ሰንበት ይባላሉ፡፡ የእመቤት አሠሪ ሲሆኑ በንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ ወ/ሪት ወይንሸትን ስለእመቤት ሥራው ብዙ ምን የሚነግሩን ነገር አለ? አልናቸው፡፡ እሳቸውም «እመቤት ወደእኔ የመጣችው የዛሬ ዓመት ነው፤ እኔ ቤት ከገባችበት ጊዜ ጀምሮ ለአራት ወር ያህል ብቻ ነው በሰላም /በጤና/ የኖረችው፡፡ ከባድ የራስ ምታት ነበረባት፡፡ በዚህ የተነሣ የሠራችበትን ይዛ በመሄድ ትታከማለች፡፡ ለሁለት ቀን ያህል ደህና ሆና እንደገና ይመለስባታል፡፡ በመጨረሻ ደህና ሐኪም ቤት ሂጂና ታከሚ ብዬ ከዘመድ ጋር አያይዤ ላክኋት፡፡ ሄዳ ስትመረመር የማኅፀን ዕጢ ነው አሏት፡፡ ኦፕሬሽን ለማድረግ ቀነ ቀጠሮ ሰጥተዋት በተባለው ጊዜ ሲታይ «ዕጢው ማሙቶ ብዙ ደም ፈሷልና አደጋ አለው» ብለው ወደ ካንሰር እንደተቀየረ ነገሯት፡፡ ማስታገሻ ብለው እያንዳንዱ አንድ መቶ ሰባ ብር የሚገዛ ሰባት መርፌ አዘዙላት፡፡ መርፌውንም ተወግታ መዳን አልቻለችም፤ በመጨረሻ ተስፋ ቆርጣ «በቃ ወደ ሀገሬ ላኪኝ፤ ዶክተሩ ካንሰር ነው ሲል ስለ ሰማሁት ካንሰር ደግሞ ይገድላልና አልድንም ልሂድ፤» አለችኝ» ነበር ያሉት፡፡

እመቤት የመዳኗ ተስፋ ተሟጦ ወደ ሀገሬ ልሂድ ብትልም ወ/ሪት ወይንሸት ግን ሌላ መፍትሔ ከመሻት በቀር ወደ አገሯ ለመላክ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ እንዲህ ነበር ያሏት፤ «ወደ ሀገርሽ ከመሄድሽ በፊት ለሰባት ቀን ጻድቃኔ ማርያም ሄደሽ ጠበል ትጠመቂያለሽ» እያሏት ሳለ በአጋጣሚ አዲስ አበባ ቃልቲ ቁስቋም ጠበል መጀመሩን ሰምተው ወደዚያው ወስደዋት ሁለት ወር እንደተጠመቀች አመልክተዋል፡፡ «ሁለት ወር ስትጠመቅ የማይወጣ ነገር የለም፡፡ ሁሉንም እንኳን መጥቀስ ባልችል ሁለት እባብ፣ እንቁራሪት፣ ሁለት ሸረሪት፣ አባ ጨጓሬ ሌላ ደግሞ አባ ጨጓሬ አይሉት ረጅም ነገር ወጥቶላታል፡፡ የሚወጡት ደግሞ ከነ ሕይወታቸው ሆኖ ትንሽ ሲቆዩ ይሞታሉ፡፡ የሚገርመው ነገር ቃሊቲ ቁስቋም፣ አባ ሳሙኤልና ተክለ ሃይማኖትም ስትጠመቅ ወጥቶላታል፡፡ በተለይ የቁስቋም፣ የኪዳነ ምሕረት፣ የገብርኤልና በሃያ አንድ የእመቤታችን በዓል ዕለት የሆነ ነገር ከሆዷ ሳይወጣ አይውልም፡፡ ሲወጣ ደግሞ በቀላሉ አይወጣም ጉሮሮዋን አስጨንቆና አታግሎ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ እቤት ጠበል አምጥታ ሞቅ ሲል ትጠጣና ወዲያው ይወጣል፤ የሚወጣው ነገር እንዳይታይ መጸዳጃ ቤት ቶሎ ሄዳ ታስወጣዋለች፡፡ አንድ ጊዜ እኛ ተሰብስበን በጓሮ በኩል ትጮሃለች፤ ምንድን ነው? ብለን ስንወጣ ትልቅ አይጥ በአፏ ሲወጣ ጅራቱ ብቻ ቀርቶ ያሠቃያታል፡፡ እኔ አላይም! ብዬ ደንግጬ ልትሞትብኝ ነው በሚል ፍርሃት ጎረቤቴን ስልክ ደውዬ ድረስልኝ አልኩት፤ እሱ መጥቶ በዕቃ አድርጎ ለሦስት ቀን ያህል አስቀመጠው፡፡ መጥፎ ጠረን ሲያመጣና እሷም አታሳዩኝ ስትል አውጥቶ ጣለው፡፡ ከዚያ በፊት ሁለት እባብ ይዛ አምጥታ አሳይታናለች፡፡ በጆሮዋና በአፍንጫዋ ሳይቀር ሙልጭ ሙልጭ የሚል አልቅት ሲወጣ አይቻለሁ፡፡ በመጨረሻ ጥቅምት 30 ቀን 2002 ዓ.ም ሁለት እንቁላል ሁለት ሸረሪት ወጣላት፡፡ ይህ እንግዲህ መርዙን ነቅሎ ሲወጣ ነው» ሲሉ ድርጊቱን በአግራሞት ተርከውታል፡፡

ወ/ሪት ወይንሸት እንደገለጹት የሚወጡት ነፍሳት አቅሟን ስለሚያደክሙት ምንም ዓይነት ምግብ እንደማትወስድ ተናግረዋል፡፡ «በአፍ የምትመጠጥ ግሉኮስ እየገዛሁ ነበር የምትወስደው እንጂ ምግብ የሚባል ገና ሲሸታት አታሳዩኝ ትላለች፡፡ የተባበሩት ነፍሳት በሆዷ ውስጥ ጎጆ ሠርተው ደሟን እየመጠጧት ኖረው ነበር» በማለት ተናግረዋል፡፡

እመቤትን ያማት የነበረው በሽታ መነሻ ምን እንደሆነ የሚያውቁት /የሰሙት/ ነገር ይኖር ይሆን ማለታችን አልቀረም፡፡ ወ/ሪት ወይንሸት መልስ አላቸው፡፡ «አጀማመሩን በተመለከተ ጠበል ቦታ ለፍልፋለች፡፡ ትውልድ ሀገሯ ነው፤ መነሻውን፤ /ድርጊቱን/ ስሰማው የተቀናበረ ነገር ነው፡፡ ስለ መዳኗ እንጂ ሌላውን ብንተወው መልካም ነው» ብለዋል፡፡

ሌላው ያነጋገርነው የወ/ሪት ወይንሸትን ወንድም አቶ ብንያም ወልደ ሰንበትን ነው፡፡ እሱም ያየውንና የተገነዘበውን እንዲህ ገልጾታል፡፡ «እኔ የምናገረው ያየሁትን ሲሆን በወሬ ደረጃ የሚታመን አይደለም፡፡ እኔ እንዳውም ይሄ ምን ተብሎ ይነገራል፤ ዋናው መዳኗ ነው ብዬ ነበር፡፡ እመቤት ግን «እግዚአብሔር ያደረገልኝን ቸርነት ድንቅ ተአምሩን ሰው እንዲያውቅልኝ መመስከር አለብህ» ብላ ስለጠየቀችኝ ነው፡፡ ስለወጣላት ነገር ብዙ ተብሏል፤ እኔ ለመጨመር የምፈልገው ያልተጠቀሰውን ሲሆን ሌሎች የወጡላት እንዳሉ ሆነው ቀንድ አውጣና የኩሬ ውኃ የሚመስል ወጥቶላታል፡፡ እንደዚሁም የአባ ሳሙኤል ንግሥ ዕለት እምነት ይዘንላት መጥተን እሱን ወስዳ ጢንዚዛና ደም አይሉት ውኃ የእንቁላል አስኳል የሚመስል ነገር ወጥቶላታል፡፡ ነገሩ ከአእምሮ በላይ ነው፡፡ በሰው ሆድ ውስጥ ይህ ሁሉ ይቻላል? የሚለውን ሳስብ ይከብደኛል፡፡ ጠበል ምን ያህል ኃይል እንዳለው ያየሁትም በዚህች ልጅ ላይ ነው፡፡ እኔ ከዚህ በፊት ለጠበል የጠበቀ ዕውቀት የለኝም፤ በጠበል ሰው ተፈወሰ ሲባል ትኩረት አልሰጥም ነበር፡፡ አሁን ግን በማየቴ ለሌላውም እየመሰከርኩ ነው፡፡ የእሷን መዳን ሳይ እንደገና የመፈጠር ያህል ነው የምቆጥረው» በማለት አቶ ቢንያም አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡

ወጣት እመቤት ሥራው ብዙንና አሠሪዎቿን ካነጋገርን በኋላ «ማን ያርዳ የቀበረ፤ ማን ይናገር የነበረ» እንዲሉ ያመራነው ወደ አቶ ንጉሤ ዐምደማርያም ቤት ነው፡፡ እሳቸውም የተገነዘቡትን በእንዲህ መልኩ ነበር የገለጹት፡፡ «እመቤት ሲያማት እየተጠራሁ እመጣለሁ፤ ከእመቤት ሆድ ብዙ ነገር ይወጣል፡፡ ለምሳሌ አይጥ ሲወጣላት በተግባር አይቻለሁ፤ አንስቼም በዕቃ ያስቀመጥኩት እኔ ነኝ፡፡ የተጨቀጨቀ ግራዋ የሚመስል ነገር ሲወጣም አይቼያለሁ፡፡ ብዙ ጊዜ ያማታል፤ መድኃኒት ግዛላት በሚሉኝ ጊዜም የምገዛላት እኔ ነበርኩ፡፡ በተለይ በአፍ የሚመጠጠውን ግሉኮስ የምገዛላት እኔ ነኝ፡፡ እናም ልነግርህ የምፈልገው እኔ ክርስቲያን ነኝ፤ ቤተ ክርስቲያን ሄጄ ሰው ተፈወሰ ሲባል ከምሰማው ውጭ በዐይኔ አላየሁም ነበር፡፡ አሁን ግን በዐይኔ ስላየሁ ከሰው ሆድ ውስጥ አንድ ነገር አይደለም መቶ ነገር ወጣለት ቢሉኝ አምናለሁ፡፡ ሰው ደግሞ ሲነገረው ማመንና መቀበል አለበት፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ ቸርነቱ የጠበልን ኃይል እንደሚገልጥ መታመን አለበት፡፡ የእግዚአብሔርን ኃይልና ተአምሩን ደግሞ ሳይደበቅ መነገር፤ መመስከር እንዳለበት እምነታችን ግድ ይላል» ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡

እመቤትን ጠበል ካጠመቋት አባቶች መካከል በፍኖተ ሕይወት ቅድስት ማርያምና ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ቦሌ ቡልቡላ የሚያጠምቁት አባ ገብረ ጻድቅ ክፍለ ዮሐንስ እና በአባ ሳሙኤል ቤተ ክርስቲያን አባ ወልደ ማርያም ኅብስቴ ምን ይላሉ? ብለን ጠይቀናቸው ነበር፡፡ እነሱም «በእኅታችን ላይ የታየው የእግዚአብሔር ተአምር በሰው ሰውኛ ስንመለከተው ይከብዳል፡፡ ነገር ግን መጽሐፉ እንደተናገረው ለሰው የማይቻለው ለእግዚአብሔር ይቻለዋል፤ ስለሚል እውነት ሆነ፡፡ ከሰው ሆድ እባብ፣ አይጥ፣ እንቁራሪትና ሌሎች ነገሮች ወጡ ሲባል ግን ለሰው ሕሊና በጣም ከባድ ነው፡፡ ሰው እነዚህን ሁሉ ተሸክሞ ይሄዳል ወይ? የሚለውን ስናስብ መንፈሳዊ ሕሊና ካልሆነ በቀር ሥጋዊ ሕሊና ሊቀበለው የማይችል ነው፡፡ እኛ ስናጠምቅም ያየነው ነገር እንዳለ ሆኖ ያላየነውም ነገር አለ፡፡ በተለይ አባ ገብረ ጻድቅ ሰይጣኑ በላይዋ ላይ ስላለ እንዳይታይበት እያባረረ ወደ ወንዝ ወስዶ ከሆዷ ውስጥ ፍንቅል ብሎ ወጥቶ ውኃውን ሲመታው ያዩ አሉ፡፡ እኔ እያጠመቅሁ ስለነበር ለመያዝ ተከተሏት ስል ወዲያውኑ አስመልሷት ተወርውሮ ወንዝ ገባ አሉኝ፡፡ እኔ ሳጠምቃት አጋንንቱ ጮኋል፤ መተት ነኝ፤ ቡዳ ነኝ እያለ ሲለፈልፍ የያዛትም ትውልድ ሀገሯ እንደሆነ ነው፡፡ እኔ እንዳውም አእምሮዋን መልስላት የሚል ነው የጠየቅኩት፤ ለምን? አፍዝዟት ራሷን አታውቅም፤ ለሦስት አራት ቀን ራሷን ሳታውቅ ጠበል ቦታ ትተኛለች» ብለዋል፡፡

በመጨረሻ ይህ ሁሉ አውሬ በሆዷ እንዴት ሊቀመጥ ይችላል? እርስ በርሱስ ተስማምቶ ሊኖር ይችላል ወይ? የሚልም ጥያቄ አንሥተንላቸው ለዚህም ምላሽ አላቸው፡፡ «አውሬዎቹን እኮ የሚቀያይራቸው እርኩሱ መንፈስ ሰይጣን ነው፤ ሰይጣን ለሰይጣን መልእክተኛ ስለሆኑ ደሟን እየመጠጡ ተስማምተው ይኖራሉ፡፡ ሰይጣን በምትሃት ሆዷ ውስጥ በተለያየ ነገር እየተመሰለ የሚወጣው ሆዷን ቤት አድርጎ በመሥራት ነው» ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ጽሑፋችንን የምንቋጨው አባ ገብረ ጻድቅ ባስተላለፉት መልእክት ነው፡፡ እመቤትን ያስታመሟት ሰዎች እግዚአብሔር የሚያዘውን ትልቅ ሥራ ሠርተዋል፡፡ የሠሩት መልካም ሥራ ደግሞ ለሁሉም ሰው ትምህርት የሚሆን ነው፡፡ ስለዚህ ሌሎችም ሊማሩበት ይገባል፤ እያልን እግዚአብሔር ይባርካቸው፤ እሷንም ሞልቶ ይማራት እንላለን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ልቦለድየሚስጥረ ማመልከቻዎች ከጌቱ ሀይሉ

መድሃኔ Aለም ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ካለው ቤንዚን ማደያ ጋ ቆማ ታክሲ ትጠብቃለች። ሚስጥረ ትባላለች። ከቤንዚን ማደያው ጋር ተያይዛ ካለችው Aነስትኛ ቡና ቤት የሚወጡና የሚገቡ ደምበኞችዋ (Aብዛኞቹ መምህራን) Aይኖች ሳያርፉባት Aያልፉም። Eሷም ብትሆን ማስተዋሏ Aልቀረም። ሚስጥረ Aንደነዚህ ያሉትን ሰዎች "በAይንዋ ቂጥ" (በስዋ Aባባል) ነው የምትገረምማቸው።
ከወደ Aስኮ መስመር የሚመጡ ታክሲዎችን ትቃኛለች። Aጠገቧ ሊደርሱ ትንሽ ሲቀራቸው የቀኝ Aጅዋን ሌባ ጣት ትቀስራለች። ሹፌሩ በተቀመጠበት መስኮት ትይዩ ታጎነብስና (ፒያሳ) ትላለች። ወደ ግራ ስትዞር በጆሮዎቿ ትክክል የሚቀረው የተፈጥሮ ጸጉርዋ ላይ የቀጠለችው ሰው ሰራሽ ጸጉር ጉንጉኖች በህብረት ወደ ቀኝ ይዘማሉ። ወደ ቀኝ ስትዞር ደግሞ ወደ ግራ። ምናልባት ልጭንቅላቷ ላለመታዘዝ ይሆን? ብቻ ባንድነት መዝመማቸውና ቀጥ ማለታቸው ከጥቁር ቀጫጭን ሽቦዎች የተሰሩ ያስመስላቸዋል።
ሁለት ታክሲዎች ሞልተው፤ ሶስተኛዋን ውይይት ጀርባ መቀመጥ ባለመፈለግዋ ኣሳልፋ፤ በAራተኛዋ ጉዞ ጀመረች። ባካል ወደ ፒያሳ በሃሳብ ወደ ኋላ። ስራ ለመቀጠር "ማመልከቻ" ያስገባችባቸውን መስሪያ በቶችና ሁኒ<_tawoc mastawes jemerec::
"Aይ ነቢያት! Eሱን በሎ ደግሞ ነቢይ! ነቢያት ብሎ ደግሞ ለሱ ስም! ስሙን ቄስ ይጥራውና! Aንደዛሬው በቅዳሚ_ ቀን ነው Aይደል ያኔ Eነሱ መስሪያ ቤት ስመላለስ! ‘ግድ የለሽም Aስቀጥርሻለሁ’ ብሎኝ የወጣሁለት! Eማዬ ትሙት Aንደሱ የተጫወተብኝ የለም! Aይ ምላስ!መቸም ያውቅበታል። Aኔማ በቃ Aሱ ሲያወራልኝ፤ በቃ የEውነት የተቀጠርኩ መስሎ ይሰማኝ ነበር። ምንዋ ሞኝ ነበርኩ ግን!
’ፈተና Aዘጋጅ ኮሚቴው ውስጥ ስላለሁበት ምንም Aትስጊ። በኔ ጣይው…’ ቅብጥርሶ ሲለኝ Eንዴት Aላምነው!? ማንም ቢሆን Eንዲህ ቢባል ያምናል። በሱ Aነጋገር፣ በዚያ ላይ Aለባበሱ! በቃ ልክ ባለስልጣን ነው Aኮ የሚመስለው። Aኔ ቢያንስ ቢያንስ ያንድ ክፍል ሃላፊ ይሆናል ብዬ ነበር የገመትኩት። Eረ Aሱማ ጉራው ስራ Aስኪያጅ ያስመስለዋል!
Aሁን Aሱን ትቶ ያን ኩሩሩ ድውይ ሰውዬ ማን ማኔጀር ነው ብሎ ይገምታል!? Aሁን በየነ ከዚያ ጉድ ባያወጣኝ ኖሮ ምን ይውጠኝ ነበር! Aይ በዩ ’Eንጋባ’ Aያለባይጨቀጭቀ Aሱው ይሻላል። Aግዜር ይስጠው Aሱ ባይኖረኝ ኖሮ ይኸኔ ዲቃላዬን ታቅፌ ቁጭ ብዬ Eቀር ነበር። Aይ በዩ ጤባው!
’ግዋደኛዬ ታማለችና ያን ሆስፒታል የሚሰራውን ግዋደኛህንAስችግርልኝ’ስለው፤’የትዋ?’Aንክዋን Aላለም። ግዋደኛውስራሱ ቢሆን ጥሩ ሰው ነው። ’ያንድ ቀን ስህተት ነው፤ ለበዩ Aትንገርብኝ፤ ችግሩ የራሴ_ ነው።’ስለው ’Aሺ’ ማለቱ። ግን ለበየነ ነግሮት ይሆን? Aልነገረውም። ነግሮትማ ቢሆን ኖሮ!
ግን ነግሮት ቢሆንስ ኖሮ፤ ምን Eንዳያደርገኝ! Aይፈልጠኝ፤ Aይቆርጠኝ!ግፋ ቢል መለያየት ነው! ላልጠፋ ወንድ! ግን Aሱው ሳይሻለኝ Aይቀርም። ምንም ቢሆን በወር ድሞዝ በተቀበለ ቁጥር የሚገዛልኝ ሽቶ፣ትያትር፣ሲኒማ መጋበዙ ራሱ፤ስንት ነገር Aለ!
Aንዳንዶቹማ ደረቆች! ጠብም Aይላቸው! በዩ ግን የምጠላበት ጸባዩ ’Aት ሊስት’ በሳምንት Aንዴ Aንኳን ’ናዪት ክለብ’ Eንግባ ብሎኝም Aያውቅም። ’ፓርቲ Eንሂድ’ስለው ከስንት Aንድ ቀን ነው የሚስማማው።’ዛሬ ፕሮግራሜ ….’የሚል ፈሊጥ Aለው።"
Eሱን ደስ የሚለው በየወሩ ገንዘቡን Eየከሰከሰ መደርደሪያ ሙሉከ ገጠገጠው መጽሃፍት Aንዱን Aንስቶ፤’ሚስጥር ይህቺን Aንብቢያት፤ ባለፈው ሰሞን የወጣች ቆንጆ መጽሀፍ ናት።’ማለት ነው። Eኔ ለራሴ Aንደማንበብ የሚያስጠላኝ የለም። ሳነብ Aንቅልፌ ይመጣብኛል።"
‘Eንቁላል ፋብሪካ’ Aየተባለ የሚጠራው Aካባቢ ደርሰው፤’ወራጅ ፣ ወራጅ Aለ!’ብሎ Aንዱ ተሳፋሪ ለመውረድ ታክሲዋ ስታቆም ነበር ከሃሳብዋ የነቃችው። ወዲያውታክሲዋ በርዋን ዘግታ ጉዞ ከመጀመርዋ ወደ ትውስታዋ ተመለሰች። ጎረምሳው የታክሲ ሹፌር ጉሮሮውን Aየጠራረገ ንግግር ለመክፈት ቢሞክርም Aልሰማችውም።
"ትሩፋት፤ ትሩፌ ነች ነብያት መዝገብ ቤት Aንደሚሰራ የነገረችኝ። ጎበዝ ናት።ፈተናውን Aልፋ የተቀጠረችው Eሷው ናት። ምነው የሷን ጭንቅላት ቢሰጠኝ! ነቢያት ሺፈራው የመዝገብ ቤት ጸሀፊ። ድንቄም የፈተና Aዘጋጅ ኮሚቴ Aባል! ከነቢያትስ ደመቀ ይሻላል። Eውነቴን ነው፤ ገገማ ቢሆንም ቁርጡን የሚናገረው ይሻላል። Aንደ ነቢያት ቀልጣፋ ቢሆንማ ኖር ይሄኔ_ ስንትዋን ያወጣ ነበር! ገና Aንድ ሁለት ቃላት ከመለዋወጣችን፤ ’የኔ Eህት ልረዳሽ የምችል Aይመስለኝም። መስሪያ ቤታችንም ቢሆን በዘመድ Aዝማድ የሚሰራበት Aይነት Aይደለም። ሊ_ላው ቢቀር በኔ በኩል የማይሆን ነገር ነው። ቦታው መመዘኛውን ለሚመጥን ማንኛውም Iትዮጵያዊ ክፍት ነው። ፈተና Eንሰጣለን፤ Aናወዳድራለን ማለት ነው። የውድድሩ Aሸናፊ ይቀጠራል። በዚህ መሰረት ነው ያንቺንም ጉዳይ የምመለከተው።’Aለኝ። ገገማ ነው።Aኔ ነኝ ያስተካከልኩለት፤ Eሱማ Aንደዚህ መናገርም Aይችልበትም።’ …............. ’በሳቅ ጦሽ ልል ምንም Aልቀረኝ! መቼስ ምን ላድርግ ለቅጥር Aመልካች Aይደለሁ፤ Aንደምንም ቻልኩት። በኋላ በዩ ነገረኝ ስድስት ኪሎ ማኔጅመንት ግራጁæየት ነው ብሎ። ከበየነ ጋር Aንድ ሁለት ቀን Aይቶኝ Aይደል ’…ሜሲሪያ ቤታቺኒ …’ያለው። በትውውቅ Aንደማይጠቅመኝ ማስጠንቀቁ ነው በሱ ቤት። ራሱ በየነስ ራሱ በየነስ ቢሆን ’ለምንልኝ’ብለው ’Eምቢ’ Aይደል ያለው! ’ፕሪንሲፕል’የሚሉት ነገር Aላቸው። Aይ ደመቀ! የኛ ሃቀኛ!’ኮከብ ሰራተኛ’ተብሎ ይሸለማታ!ግን ቢሆንም Eስው ቁርጤን የነገረኝ ይሻለኛል። ያኔማ ለፈተናም Aልሄድኩ፤ ላላፍ ነገር።
ራስ ደስታ ሆስፒታል Aካባቢ ሲደርሱ የታክሲው ሹፌር ሌላ የካሴት ክር Aስገባ።ሚስጥረን ’ካረቢያን ኪዊን’ የሚለው ሙዚቃ ወደ ለላ ትውስታ ቀየራት። የሹፌሩAይኖች Aጭሩ ጅንስ ቀሚስ በከፊል ያጋለጣቸው፤ ከጉለበቶችዋ በላይ Eስክ ቀሚሱ ጠርዝ ድረስ ያለው የሰውነት ክፍልዋ ላይ Aርፈዋል።Aላስተዋለቸቻቸውም።
"Aይ ዳኒ! ይሄኔ Aንተ Aሜሪካን ሀገር ተንደላቀህ ትኖራለህ። Eኔ Eዚህ በዚህ ሙዚቃ ሁሌ Aስታውስሃለሁ።’ካረቢያን ኪዊን’የሚለውን ቀይረህ ’Iትዮጵያን ኪዊን’Eያልክ ስትዘፍንልኝ የነበረው Aይረሳኝም። የሽኝትህ ቀን ዋዜማ ፌርዌል ላይ ስንት ጊዜ Eንደደነስንበት፤ ያልከኝ ሁሉ Aይረሳኝም።ይሄኔ Aንተ Eንክዋን ዘፈኑን Eኔንም ረስተህኝ የሆናል። Aይ ዳኒ! ’ዳኒ ቦይ በይኝ ስትጠሪኝ’ ያልከኝ ትዝ የልሃል?Eዚያ መቼም ’ዳኒ ቦይ’ Eያሉ ነው የሚጠሩህ። ’ሄሎው ዳኒ ቦይ! ሃው ዱ ዩ ዱ!’ Eንዴት ደስ ይላል!ታድለህ!Eኔም Aንድ ቀን ከዚች ሃገር መውጣቴ Aይቀር! ዳኒ ቃሉን ካላጠፈ ወደ Aሜሪካ Eወስድሻለሁ ብሎኝ ነበር። ቢሆን ነው Eንጂ ታድያ Eስከ ዛሬ ፖስት ካርድ Eንኳን ሰው Aይልክም?!
ቢሳካልኝማ ስራ፣ ምናምን ከማለት መውጣቱ ነበር የሚሻለኝ።"
’ካረቢያን ኪዊን’ Aብቅቶ ወደ ሌላ ትውስታ፤ ወደ ዋናው መለሳት። ግራ Eግርዋ ላይ የጫነችውን የቀኝ Eግርዋን Aውርዳ ግራ Eግርዋን የቀኝ Eግርዋ ላይ ጫነችው። የታክሲ ሹፌሩ Aይኖች Aረፉባቸው። Aላስተዋለቸቻቸውም።
"ከሁሉም የተጫወተብኝ ግን ደጀኔ ነው። Eሱ Eንደሸወደኝ ማንም Aልሸወደኝም። Eንደ ነበያት ስልጣን Aጥቶ Aይደለም። የሰራተኛ ክፍል ሃላፊ ነው Aሉ። ማስቀጠር ቢፈልግ በደንብ ይችል ነበር። መዸመርያ ጥሩ ሰው መስሎ ኋላ ማለት Aመጣ Eንጂæ^። ’Aይዞሽ ሚስጥረ ሁሉንም ነገር በኔ ጣይው፤Oኬ!’ከዚያ Eጆቹን ጠረጴዛ ላይ ደግኖ፤ ጣቶቸን Eያፍተለተለ፤ ቅንደቦቹን ሸብሽቦ፤ ከናፍሩን ወደፊት Eየለጠጣቸው፤ ’ግን ሚስጥረ Eንደምታውቂው Aንድ ሰው ላንድ ሰው Aንድን ጉዳይ ሲፈጽምለት በሌላ ጊዜ ያ ሰው፤ ማለቴ ጉዳዩ የተፈጸመለት ሰው በተራው ያን የፈጸመለትን የሚረዳበት ሁኔታ፣ መንገድ ካገኘ ወደ ኋላ Eንደማይል የምታውቂ የመስለኛል። Eና ተግባባን?….’Eኔ ልዽት Eንኳን ይህችንና የዝንብ ምንትስ Eናውቃለን Aልኩና በልቤ፤ ባፌ ’Eሺ!’ነዋ! መጀመሪያ Eኔ የሱ ጉዳይ ፈጻሚ ሆንኩ። Eሱ Eኔ Eርዳታ በምፈልግበት ጊዜ ወደ ኋላ Eንደማይል ሙሉ በሙ=ሉ በመተማመን። Aይ ደጀኔ! መጨረሻ ላይ ምናለኝ ታድያ?!’ሚስጥረ ምንም ማድረግ Aልችልም። ፍቅር ሌላ፤ ስራ ማስቀጠር ሌላ።’Aይን Aውጣ ደረቅ!Eሱን ብሎ ሃቀኛ!ስንትዋን Eንዲህ ብልዋት ይሆን? ታድያ ከሱ ደመቀ Aይሻልም?"
ታክሲዋ የማዘጋጃ በት ዋናው በራፍ ጋ ልትደርስ ትንሽ ሲቀራት ቆመችና ተሳፋሪዎችዋን ማራገፍ ጀመረች። ምንም Eንኳን ከስልሳ ሳንቲም በላይ የሚሆኑ ዝርዝር ፍራንኮች ቢኖርዋትም ሰሞኑን የምትመላለስበት መስሪያ ቤት ያስቀጥሩኛል ብላ ተስፋ የጣለችባቸውና ለዛሬ የቀጠሯትን የመስሪያ ቤቱን ምክትል ስራ Aስኪያጅ AEምሮዋ ውስጥ Aስገብታ ነበርና ቦርስዋን ከፍታ፤ ከተጣጠፉት ብሮች መሃከል Aንድዋን መዛ Aውጥታ ሰጠችው።
ሹፌሩ Aሁንም Aጭሩ የጅንስ ቀሚስ ወጥሮ ከያዘው ሰውነትዋ ላይ Aይኖቹን ሳይነቅል ተቀበላት። ከታክሲዋ ወርዳ መልስዋን ስትቀበል፤ AEምሮዋ ያለፉትን ጊዚያት ትቶ ላሁኑ ጊዚያት ክፍት ቦታ ስያገኝ፤ ሹፌሩን Aወቀችው። ’ጂ ሰ ስ!’ Aለች በሆድዋ። በሩን ’ጠርቅማበት’ Eርምጃዋን ቀጠለች።
Aሁንም የጎረምሳው ሹፌር Aይኖች ከበስተ ኃላዋ መቃኘታቸውን Aልተዉም። ከወራት በፊት የመዝገብ ቤት ጸሀፊ የነበረው፤ በAሁኑ ጊዜ ቤተሰቦቹ የገዙለትን ’ውይይት’ ታክሲ የሚያሽከረክረው የነቢያት ሺፈራው Aይኖች።
Aሁንስ ባታያቸውም Aስተውላቸዋልች።
ከጌቱ ሀይሉ

About Me